top of page

የጁላይ 2025 (እ.ኤ.አ.) የአማራ ጦርነት ማጠቃለያ

  • Writer: AAA-admin
    AAA-admin
  • 10 minutes ago
  • 1 min read

ነሐሴ 15 ቀን 2017 (ኦገስት 21፣ 2025) 


ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2017 (ከጁላይ 1 እስከ 31 ቀን 2025) በ104 የተለያዩ ወረዳዎች/ከተማ አስተዳደሮች በ18 የዞን አስተዳደሮች (በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና አዲስ አበባ ከተማ) ውስጥ የተለያዩ ውጊያዎች እና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተመዝግበዋል።


በፈረንጆች ጁላይ ወር በተለያዩ ወሳኝ አካባቢዎች ከፍተኛ ወታደራዊ ጉዳት የደረሰባቸው እና የቁጥጥር ሚዛን ለውጥ የተደረጉባቸው ውጊያዎች ተካሔደዋል። በዚህ ወር የአማራ ፋኖ ራስን የመከላከያ ኀይል ከኦሮሞ ብልጽግና ፖርቲ አገዛዝ ጥምር ኀይሎች ጋር ሰፊ ውጊያዎችን አድርገዋል።


ዘገባው በተሰራበት ጊዜ ውስጥ በ92 ወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች በ15 የዞን አስተዳደሮች ውስጥ (አማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች) የተካሄዱ 213 ውጊያዎች ተመዝግበዋል። በዚኽም 5,284 የአገዛዙ ኀይል አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል እና 121 የፋኖ አባላት ጉዳት የደረሰባቸው ተመዝግበዋል።


ree

 

ree

ዘገባው በተሰራበት ጊዜ ውስጥ በ40 ወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች በ15 የዞን አስተዳደሮች በ3 ክልሎች (በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና አዲስ አበባ ከተማ) 55 የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ተመዝግበዋል። በዚኽም

  • 149 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል፤

  • 96 ሰላማዊ ሰዎች ቆስለዋል፤

  • 15 እገታዎች እና

  • 357 እስራቶች ተመዝግበዋል።

ree
ree

በርካታዎቹ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች በኦሮሞ ብልጽግና አገዛዝ ኀይሎች የተፈጸሙ ሲሆን የተወሰኑት ወንጀሎች የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሃይል፣ «ኤርፔ» ታጣቂዎች፣ ቄሮ፣ በትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) እና ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ተፈጽመዋል።


ree

 
 
 

Share this  site on Twitter

  • Facebook
  • Twitter

©2021 by Amhara Association of America.

bottom of page