የኦገስት 2025 (እ.ኤ.አ.) የአማራ ጦርነት ማጠቃለያ
- AAA-admin

- Sep 27
- 1 min read
መስከረም 16 ቀን 2018 (ሴፕቴምበር 26, 2025)
ከሐምሌ 25 እስከ ነሐሴ 25 ቀን 2017 (ከኦገስት 1 እስከ 31 ቀን 2025) በ106 የተለያዩ ወረዳዎች/ከተማ አስተዳደሮች በ18 የዞን አስተዳደሮች (በአማራ እና ኦሮሚያ) ውስጥ የተለያዩ ውጊያዎች እና የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ተመዝግበዋል።
በፈረንጆች ኦገስት ወር በተለያዩ ወሳኝ አካባቢዎች ከፍተኛ ወታደራዊ ጉዳት የደረሰባቸው እና የቁጥጥር ሚዛን ለውጥ የተደረጉባቸው ውጊያዎች ተካሔደዋል። በዚህ ወር የአማራ ፋኖ ራስን የመከላከያ ኀይል ዋና ዋና የክፍለ ሀገር ኮማንዶች አንድነት የፈጠሩ ሲሆን ከኦሮሞ ብልጽግና ፖርቲ አገዛዝ ጥምር ኀይሎች ጋር ሰፊ ውጊያዎችን አድርገዋል።
ዘገባው በተሰራበት ጊዜ ውስጥ በ96 ወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች በ16 የዞን አስተዳደሮች ውስጥ (በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች) የተካሄዱ 235 ውጊያዎች ተመዝግበዋል። በዚኽም 4,485 የአገዛዙ ኀይል አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል እና 118 የፋኖ አባላት ጉዳት የደረሰባቸው ተመዝግበዋል።


ዘገባው በተሰራበት ጊዜ ውስጥ በ41 ወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች በ16 የዞን አስተዳደሮች በ2 ክልሎች (አማራ እና ኦሮሚያ) 73 የሰብአዊ መብት ረገጣዎች ተመዝግበዋል። በዚኽም
111 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል፤
78 ሰላማዊ ሰዎች ቆስለዋል፤
4 እገታዎች እና
2,528 እስራቶች ተመዝግበዋል።


በርካታዎቹ የሰብአዊ መብት ረገጣዎች በኦሮሞ ብልጽግና አገዛዝ ኀይሎች የተፈጸሙ ሲሆን የተወሰኑት ወንጀሎች በትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትሕነግ) ፤ የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሃይል፤ እና ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች ተፈጽመዋል።













Comments