top of page
  • Writer's pictureAAA-admin

የዐማራ ፋኖ ትጥቅ መፍታት እና የዐማራ ልዩ ኃይል መፍረስ የዐማራ ህዝብ የህልውና አደጋ የመጨረሻው ደረጃ ነው።

ከዓለም አቀፍ የዐማራ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ!

መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓመተ ምህረት


የአብይ አህመድ ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ዐማራ ጠል አቋሙን በሰፊው በመግፋት አሁን የደረሰበት ደረጃ አይነተኛ ማሳያው የዐማራ ፋኖን ትጥቅ ማስፈታት እና የዐማራ ልዩ ኃይልን ማፍረስ ነው። በተለይም የዐማራ ፋኖን ትጥቅ ለማስፈታት እና የዐማራ ልዩ ኃይልን ለማፍረስ የተነሳበትም ጊዜ፦


  • ትህነግ ከነሙሉ ትጥቁ ተጨማሪ ሠራዊት እያሰለጠነ ባለበት፣

  • ኦነጋዊያን ዐማራውን ፈጽሞ ለማጥፋት አቅደው እና ሰንደው በተነሱበት፣

  • የሱዳን የጦር ሀይል የኢትዮጵያ እና የዐማራ ክልልን ዘልቆ በወረረበት፣

  • ዐማራውን በኦሮሞ ክልል መጨፍጨፉ እና ማሳደዱ በቀጠለበት፣